وَالتِّينِ وَالزَّيْتُونِ (1)

በበለስና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡

وَطُورِ سِينِينَ (2)

በሲኒን ተራራም፤

وَهَٰذَا الْبَلَدِ الْأَمِينِ (3)

በዚህ በጸጥተኛው አገርም (እምላለሁ)፡፡

لَقَدْ خَلَقْنَا الْإِنْسَانَ فِي أَحْسَنِ تَقْوِيمٍ (4)

ሰውን በጣም በአማረ አቋም ላይ ፈጠርነው፡፡

ثُمَّ رَدَدْنَاهُ أَسْفَلَ سَافِلِينَ (5)

ከዚያም (ከፊሉን) ከዝቅተኞች ሁሉ በታች አድርገን መለስነው፡፡

إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ فَلَهُمْ أَجْرٌ غَيْرُ مَمْنُونٍ (6)

ግን እነዚያ ያመኑት መልካሞችንም የሠሩት ለእነርሱ ተቆራጭ ያልኾነ ምንዳ አልላቸው፡፡

فَمَا يُكَذِّبُكَ بَعْدُ بِالدِّينِ (7)

ታዲያ ከዚህ በኋላ በፍርዱ ምን አስተባባይ አደረገህ?

أَلَيْسَ اللَّهُ بِأَحْكَمِ الْحَاكِمِينَ (8)

አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን? (ነው)፡፡