وَالشَّمْسِ وَضُحَاهَا (1)

በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡

وَالْقَمَرِ إِذَا تَلَاهَا (2)

በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤

وَالنَّهَارِ إِذَا جَلَّاهَا (3)

በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤

وَاللَّيْلِ إِذَا يَغْشَاهَا (4)

በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤

وَالسَّمَاءِ وَمَا بَنَاهَا (5)

በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤

وَالْأَرْضِ وَمَا طَحَاهَا (6)

በምድሪቱም በዘረጋትም፤

وَنَفْسٍ وَمَا سَوَّاهَا (7)

በነፍስም ባስተካከላትም፤

فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَاهَا (8)

አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡

قَدْ أَفْلَحَ مَنْ زَكَّاهَا (9)

(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡

وَقَدْ خَابَ مَنْ دَسَّاهَا (10)

(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡

كَذَّبَتْ ثَمُودُ بِطَغْوَاهَا (11)

ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡

إِذِ انْبَعَثَ أَشْقَاهَا (12)

ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡

فَقَالَ لَهُمْ رَسُولُ اللَّهِ نَاقَةَ اللَّهِ وَسُقْيَاهَا (13)

ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡

فَكَذَّبُوهُ فَعَقَرُوهَا فَدَمْدَمَ عَلَيْهِمْ رَبُّهُمْ بِذَنْبِهِمْ فَسَوَّاهَا (14)

አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡

وَلَا يَخَافُ عُقْبَاهَا (15)

ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡