وَالسَّمَاءِ وَالطَّارِقِ (1)

በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡

وَمَا أَدْرَاكَ مَا الطَّارِقُ (2)

የሌሊት መጪውም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

النَّجْمُ الثَّاقِبُ (3)

ጨለማን ቀዳጁ ኮከብ ነው፡፡

إِنْ كُلُّ نَفْسٍ لَمَّا عَلَيْهَا حَافِظٌ (4)

ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡

فَلْيَنْظُرِ الْإِنْسَانُ مِمَّ خُلِقَ (5)

ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፡፡

خُلِقَ مِنْ مَاءٍ دَافِقٍ (6)

ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ፡፡

يَخْرُجُ مِنْ بَيْنِ الصُّلْبِ وَالتَّرَائِبِ (7)

ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ)፡፡

إِنَّهُ عَلَىٰ رَجْعِهِ لَقَادِرٌ (8)

እርሱ (አላህ) በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡

يَوْمَ تُبْلَى السَّرَائِرُ (9)

ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን፡፡

فَمَا لَهُ مِنْ قُوَّةٍ وَلَا نَاصِرٍ (10)

ለእርሱም (ለሰው) ኀይልና ረዳት ምንም የለውም፡፡

وَالسَّمَاءِ ذَاتِ الرَّجْعِ (11)

የመመለስ ባለቤት በኾነችው ሰማይም እምላለሁ፡፡

وَالْأَرْضِ ذَاتِ الصَّدْعِ (12)

(በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በኾነችው ምድርም፤

إِنَّهُ لَقَوْلٌ فَصْلٌ (13)

እርሱ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ ቃል ነው፡፡

وَمَا هُوَ بِالْهَزْلِ (14)

እርሱም ቀልድ አይደለም፡፡

إِنَّهُمْ يَكِيدُونَ كَيْدًا (15)

እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ይሠራሉ፡፡

وَأَكِيدُ كَيْدًا (16)

(እኔ) ተንኮልንም እመልሳለሁ፡፡

فَمَهِّلِ الْكَافِرِينَ أَمْهِلْهُمْ رُوَيْدًا (17)

ከሓዲዎችንም ቀን ስጣቸው፡፡ ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው፡፡