وَالسَّمَاءِ ذَاتِ الْبُرُوجِ (1)

የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡

وَالْيَوْمِ الْمَوْعُودِ (2)

በተቀጠረው ቀንም፤

وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ (3)

በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡

قُتِلَ أَصْحَابُ الْأُخْدُودِ (4)

የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡

النَّارِ ذَاتِ الْوَقُودِ (5)

የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡

إِذْ هُمْ عَلَيْهَا قُعُودٌ (6)

እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡

وَهُمْ عَلَىٰ مَا يَفْعَلُونَ بِالْمُؤْمِنِينَ شُهُودٌ (7)

እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡

وَمَا نَقَمُوا مِنْهُمْ إِلَّا أَنْ يُؤْمِنُوا بِاللَّهِ الْعَزِيزِ الْحَمِيدِ (8)

ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡

الَّذِي لَهُ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ وَاللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ شَهِيدٌ (9)

በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡

إِنَّ الَّذِينَ فَتَنُوا الْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ ثُمَّ لَمْ يَتُوبُوا فَلَهُمْ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمْ عَذَابُ الْحَرِيقِ (10)

እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡

إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَهُمْ جَنَّاتٌ تَجْرِي مِنْ تَحْتِهَا الْأَنْهَارُ ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْكَبِيرُ (11)

እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡

إِنَّ بَطْشَ رَبِّكَ لَشَدِيدٌ (12)

የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡

إِنَّهُ هُوَ يُبْدِئُ وَيُعِيدُ (13)

እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡

وَهُوَ الْغَفُورُ الْوَدُودُ (14)

እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡

ذُو الْعَرْشِ الْمَجِيدُ (15)

የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡

فَعَّالٌ لِمَا يُرِيدُ (16)

የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡

هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ الْجُنُودِ (17)

የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?

فِرْعَوْنَ وَثَمُودَ (18)

የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡

بَلِ الَّذِينَ كَفَرُوا فِي تَكْذِيبٍ (19)

በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡

وَاللَّهُ مِنْ وَرَائِهِمْ مُحِيطٌ (20)

አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡

بَلْ هُوَ قُرْآنٌ مَجِيدٌ (21)

ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡

فِي لَوْحٍ مَحْفُوظٍ (22)

የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡