قُلْ أَعُوذُ بِرَبِّ الْفَلَقِ (1)

በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡

مِنْ شَرِّ مَا خَلَقَ (2)

«ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት፡፡

وَمِنْ شَرِّ غَاسِقٍ إِذَا وَقَبَ (3)

«ከሌሊትም ክፋት ባጨለመ ጊዜ፤

وَمِنْ شَرِّ النَّفَّاثَاتِ فِي الْعُقَدِ (4)

«በተቋጠሩ (ክሮች) ላይ ተፊዎች ከኾኑት (ደጋሚ) ሴቶችም ክፋት፡፡

وَمِنْ شَرِّ حَاسِدٍ إِذَا حَسَدَ (5)

«ከምቀኛም ክፋት በተመቀኘ ጊዜ፤ (እጠበቃለሁ በል)፡፡»